የሀብት ማፈላለግና ማስተላለፍ

 

የሀብት ማፈላለግና ማስተላለፍ አንድ ራሱን የቻለ ቡድን ሲሆን፣ ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት ኃላፊነቱን ወስዷል፡-

  • የኤችአይቪ/ኤድስ ፕሮግራሞችን ለመደገፍ ፈቃደኞች የሆኑ ምንጮችን በመለየት ግንኙነቶች መመስረት፣
  • በከተማው ውስጥ በመስራት ላይ ላሉ ልዩ ልዩ የሚተገብሩ አጋሮች የገንዘብ ድጋፍ መስጠት፣
  • በሃብቶች ማደራጀት ስትራቴጂ እና በገንዘብ አጠቃቀም ቴክኒኮች ረገድ ስልጠና መስጠት
  • የሃብቶች ማፒንግ ትንተና ማካሄድ (በፕሮግራም እንዲሁም በሰው ሃይል፣ በማቴሪያል እና በፋይናንስ ክፍተቶች)
  • የሃብት ማደራጀት ስትራቴጂ እና የክፍተት ትንተና ማጐልበት
  • የሃብት ማደራጀት መድረኮች ማደራጀት
  • የፕሮጀክት ግምገማ ማከናወን
  • የሃብቶች ማደራጀት መመሪያ ማጐልበት እና/ወይም ተግባራዊ ማድረግ
  • ገንዘብ ረጂ ኤጀንሲዎችን በመለየት ገንዘብ ለማሰባሰብ እንዲረጃ የፕሮጀክት ፕሮፖዛል ማዘጋጀት
  • የፕሮጀክት አቅም ግምገማ ቼክሊስት ማዘጋጀት
  • ለተግባሪ አጋሮች ማለትም አይፒ፣ ሲቢኦ እና ኤፍቢኦ የአቅም ግምገማ ማካሄድ
  • ሃብቶችን በማሰራጨት የተመደቡትን ገንዘቦች መክፈል እንዲሁም ለሴክተር ቢሮዎች መመደብ፣ አይፒኤስ፣ ሲቢኦ እና ኤፍቢኦ
  • የገንዘብ ድጋፍ ለመስጠት ለፀደቁ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ ስምምነት ሰነዶች ማዘጋጀት
  • የፕሮጀክት የሶስትዮሽ ስምምነት የቴክኒክ ድጋፍ መስጠት
  • የሀብት ማፈላለግና ማስተላለፍ ቡድን በየሩብ አመቱ ለጽ/ቤቱ የሚቀርብ የእቅድ ትግበራ ሪፖርት ማዘጋጀት
  • የጽ/ቤቱን የሃብቶች መረጃ ዳታቤዝ መመስረት (በጠቅላላው የተላለፈ፣ የተደራጀ እና በከተማ ደረጃ የተሰራጨ መረጃ)
  • በሃብቶች ማደራጀት ስትራቴጂ እና በፕሮጀክት ግምገማ ሂደት እንዲሁም ከሌሎች ክልሎች ጋር ስላለው የሥራ አፈፃፀም የልምድ ልውውጥ ማድረግ
  • በሃብቶች አደረጃጀት ወይም አጠቃቀም እና በፕሮጀክት ስራ አመራር ረገድ በውጪ ሃገር እና በሃገር ውስጥ የአጭር ጊዜ ስልጠና መስጠት